ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ማዕከላዊ የአስተዳደር ሕንጻ አስመርቋል።
በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ ይህን የመሰለ ውብ ህንፃ ከነ ኢንፍራስትራክቸር በፍጥነትና በጥራት ገንብቶ በጊዜ ያስረከበው ድርጅታችን ሽልማት ተቀብሏል።
እንኳን ደስ አላችሁ፣ አለን!!!
የረዳን ፈጣሪ ይመስገን!
ፕሮጀክቱ የተገነባው በመላ አገሪቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በማድረስ ከ30 ዓመታት በላይ ልምድ ባለው በይርጋለም ኮንስትራክሺን የግንባታ ኩባንያ ነው። ኩባንያው የአስተዳደር ሕንፃዎችን፣ የንግድ ሕንጻዎችን፣ ሆስፒታሎችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ ድልድዮችን እና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በተሳካ ሁኔታ ሰርቶ አስረክቧል። ለጥራት፣ ለቴክኖሎጂና እና ለሙያ ባለው ቁርጠኝነት የሚታወቀው ይርጋለም ኮንስትራክሽን ከመንግስት ተቋማት፣ ከአማካሪዎች፣ ከመሐንዲሶች እና ከአካባቢው ማህበረሰቦች ጋር በቅርበት ይሰራል። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር የግንባታ ኮምፕሌክስ የዚህ ቁርጠኝነት ነጸብራቅ ነው።
ኮንስትራክሽን ኩባንያው ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ቁርጠኝነትን ላሳዩ የካምፓኒው አማካሪ መሃንዲሶች፣ አመራርና ማናጂመንት አካላትና ሰራተኞች በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ይህን ስራ እዉን ለማድረግ የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጉ ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል።
For all new and updates follow us on
Website: https://yirgalemconstruction.com
Facebook: https://facebook.com/yirgacons
Instagram: https://instagram.com/yirgacon
Telegram: https://t.me/yirgacon
Twitter: https://x.com/yirgacon
Youtube: https://www.youtube.com/@yirgacon
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/yirgacon
በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!
ይርጋለም ኮንስትራክሽን!











