HomeNews & Eventsይርጋለም ኮንስትራክሽን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ማዕከላዊ የአስተዳደር ሕንጻ ምርቃት ላይ ተሸለመ።

ይርጋለም ኮንስትራክሽን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ማዕከላዊ የአስተዳደር ሕንጻ ምርቃት ላይ ተሸለመ።

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ማዕከላዊ የአስተዳደር ሕንጻ አስመርቋል።

በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ ይህን የመሰለ ውብ ህንፃ ከነ ኢንፍራስትራክቸር በፍጥነትና በጥራት ገንብቶ በጊዜ ያስረከበው ድርጅታችን ሽልማት ተቀብሏል።

እንኳን ደስ አላችሁ፣ አለን!!!

የረዳን ፈጣሪ ይመስገን!

ፕሮጀክቱ የተገነባው በመላ አገሪቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በማድረስ ከ30 ዓመታት በላይ ልምድ ባለው በይርጋለም ኮንስትራክሺን የግንባታ ኩባንያ ነው። ኩባንያው የአስተዳደር ሕንፃዎችን፣ የንግድ ሕንጻዎችን፣ ሆስፒታሎችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ ድልድዮችን እና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በተሳካ ሁኔታ ሰርቶ አስረክቧል። ለጥራት፣ ለቴክኖሎጂና እና ለሙያ ባለው ቁርጠኝነት የሚታወቀው ይርጋለም ኮንስትራክሽን ከመንግስት ተቋማት፣ ከአማካሪዎች፣ ከመሐንዲሶች እና ከአካባቢው ማህበረሰቦች ጋር በቅርበት ይሰራል። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር የግንባታ ኮምፕሌክስ የዚህ ቁርጠኝነት ነጸብራቅ ነው።

ኮንስትራክሽን ኩባንያው ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ቁርጠኝነትን ላሳዩ የካምፓኒው አማካሪ መሃንዲሶች፣ አመራርና ማናጂመንት አካላትና ሰራተኞች በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ይህን ስራ እዉን ለማድረግ የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጉ ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል።

 

For all new and updates follow us on

Website: https://yirgalemconstruction.com

Facebook: https://facebook.com/yirgacons

Instagram: https://instagram.com/yirgacon

Telegram: https://t.me/yirgacon

Twitter: https://x.com/yirgacon

Youtube: https://www.youtube.com/@yirgacon

Linkedin: https://www.linkedin.com/company/yirgacon

በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!

ይርጋለም ኮንስትራክሽን!

Share:

Leave A Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Yirgacon Support

Typically replies within a day

Hello, Welcome to the site. Please click below button for chatting me through Telegram.